federal proclamations, regulations, directives, regional constitutions and laws.
You can search cases by number, volume, subject matter
Training and teaching materials, articles, legal forms, links to resources...
የሥራ ውል የተደረገው ለተወሰነ ጊዜ ወይም ሥራ ነው በሚል ክርክር በቀረበ ጊዜ ይህንኑ የማስረዳት ሸክም የሚኖር ስለመሆኑ አዋጅ ቁ. 377/96 አንቀፅ 9
Download Cassation Decision
በወንጀል ሕግ ቁጥር 543 እና 567 መሰረት አንድ ሰው በአንድ ጊዜ ሊጠየቅ ስለሚችልበት አግባብ የኢ.ፌ.ዲ.ሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 543,567
በውርስ ሕግ ውስጥ የተመለከቱ የይርጋ ድንጋጌዎች ሊተረጐሙ የሚችሉበት አግባብ የወራሽነት መብትን በሕግ በተመለከተ ጊዜ ውስጥ ያረጋገጡ ወራሾች የውርስ ንብረት ክፍፍል ጥያቄን በማናቸውም ጊዜ ማቅረብ የሚችሉ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሕ/ቁ. 996,1000(1)1002,1060,1062
በህግ /ፍርድ/ ኃይል የተወሰደ ንብረት ሊመለስ የሚችልበት አግባብ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 349/1/
ሠራተኛ የተረከባቸውን ንብረቶች አላስረከበም ወይም አጉድሏል በሚል የሥራ ውሉ በተቋረጠ ጊዜ የሚጠይቃቸውን ተገቢ ክፍያዎች ሊጠይቅ አይችልም በሚል በአሠሪው የሚቀርብ ክርክር ተገቢነት የሌለው ስለመሆኑ አዋጅ ቁ. 377/96 አንቀፅ 36 37 38
ሥራውን በገዛ ፈቃዱ የሚለቅ ሰራተኛ የስንብት ክፍያ ለማግኘት የሚችለው ቢያንስ የ5 ዓመት አገልግሎት ያለው እንደሆነ ስለመሆኑ አዋጅ ቁ. 494/98 አንቀጽ 2(ሸ)
አንድን መፅሐፍ ከተፃፈበት ቋንቋ ወደ ሌላ ቋንቋ የተረጐመ ሰው እንደ ድርሰት አመንጪ ተቆጥሮ የሞራልና የቁሣዊ ጉዳት ሊወሰንለት ስለመቻሉ አዋጅ ቁ.41ዐ/96 አንቀፅ 2(2) 6(1)
የልዩ አዋቂ ምስክሮች በፍ/ቤት የሚሾሙበት፣ የሙያ ግዴታቸውን የሚያከናውኑበት እና ፍ/ቤቶችም የሚቀርበውን ሙያዊ ምስክርነት ሊቀበሉ የሚችሉበት አግባብ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 136
ይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት የሥር ፍ/ቤትን ውሣኔ በመሻር በዋናው ጉዳይ ላይ የራሱን ውሣኔ ካሣለፈና የበላይ የሆነ ፍ/ቤት ደግሞ የይግባኝ ውሳኔውን ባለመቀበል የሥር ፍ/ቤትን ውሣኔ በደፈናው በማፅናት የሚሰጠው ውሣኔ የተከራካሪ ወገን የይግባኝ መብት የሚያጣብብና የሥነ-ሥርዓት ህግ ደንብን የሚጥስ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 341 342 343
ከውርስ ሃብት ክፍፍል ጋር በተያያዘ ተጠቃሚው በኢንሹራንስ ውል ላይ ባልተገለፀበት ጊዜ የሟች ባል ወይም ሚስት የኢንሹራንስ ገንዘቡን ከወራሾች ጋር ሊካፈሉ የሚችሉበት አግባብ የንግድ ህግ ቁጥር 705 701(1)(ሀ) የፍ/ብ/ህ/ቁ. 827
በአሰሪና ሠራተኛ ክርክር ችሎት ሠራተኛው የፈፀመው ድርጊት ከሥራ ለማሰናበት በቂ አይደለም ተብሎ መወሰኑ አሰሪው በሠራተኛው ላይ በፍ/ብሔር ጉዳይ ሊያቀርብ የሚችለውን ክስ የሚያስቀር የመጨረሻ ፍርድ /ውሣኔ/ ስላለመሆኑ
በወንጀል ድርጊት ተጠርጥሮ የተያዘ ሰው ንብረት የሆነ ንግድ መደብር ጋር በተገናኘ ፍ/ቤቶች የንግድ መደብሩን በውስጡ ከያዘው ሸቀጦች በመለየት (በመነጠል) የሚሰጡት ትዕዛዝ ተገቢነት የሌለው ስለመሆኑ
አባትነት በህግ አግባብ ሊታወቅ የሚችልባቸው ሁኔታዎች የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አንቀፅ 126 1(1) (2),128(1) 130(2) 125 106(1), የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ህገ-መንግስት አንቀፅ 35(2)
አንድ ሰው ብድሩን አለመክፈሉን አምኖ በሚከራከርበት ሁኔታ የፍ/ብሔር ህግ ቁጥር 2024(ረ) ተፈፃሚነት የማይኖረው ስለመሆኑ 2024(ረ) ዋና ብድርን ሣይሆን ለብድር የሚከፈል ወለድን የሚመለከት ስለመሆኑ
በማይንቀሳቀስ ንብረት ላይ የመያዣ መብት ውጤት የሚኖረው ከተፃፈበት ቀን ጀምሮ እስከ አሥር ዓመት ድረስ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 3058
የጉምሩክ አዋጅን በመተላለፍ ከሚፈፀም የወንጀል ድርጊት ጋር በተያያዘ የኮንትሮባንድ ተግባር ሃይልን በመጠቀም ወይም ከሌሎች ጋር በማበር የተፈፀመ እንደሆነ አዋጅ ቁ. 6ዐ/89 ተፈፃሚ ሊሆን የሚችል ስለመሆኑ
የንግድ መደብር ሽያጭ ውል በግዴታ እንዲፈፀም ለማድረግ የሚቻልበት አግባብ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 2330, 2329, 1778/
የማይንቀሳቀስ ንብረትን ለሰጠው ብድር በመያዣነት የያዘ ባለገንዘብ ባንክ መብቱ በይርጋ እስካልታገደ ድረስ የያዘውን ንብረት በጨረታ ለመሸጥ የሚገደድበት ተለይቶ በህግ የተቀመጠ የጊዜ ገደብ የሌለ ስለመሆኑ አዋጅ ቁ. 97/9ዐ አዋጅ ቁ. 216/92 አንቀፅ 2 የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ሀ/ቁ. 394 - 449
Page 68 of 116