በወንጀል ጉዳይ የተሰጠ ውሣኔ በዚያው ጉዳይ በፍትሐብሔር ክርክሩ አግባብነትና ብቃት የሚኖረው በወንጀል ክሱ ተከሳሹ በወንጀል ፍ/ቤቱ ጥፋተኛ ተብሎ የተወሰነ ከሆነና ወደዚህ ድምዳሜ ለመድረስም በወንጀሉ ጉዳይ የተሰሙት ማስረጃዎች በፍ/ብሔሩ ጉዳይም ቀርበው የተሰሙ መሆን ያለባቸው ስለመሆኑ፣
በወንጀል ጉዳይ የቀረበ ማስረጃ ለፍትሐብሔር ጉዳይ አግባብነትና ብቃት የሚኖረው በሁለቱም ጉዳዩች የተሰሙት ማስረጃዎች አንድ አይነት ሲሆኑ ስለመሆኑ፣
በወንጀልና በፍ/ብሔር ጉዳይ የተሰሙት ማስረጃዎች የተለያዩ ከሆነ እና በወንጀል ጉዳይ ክስ የቀረበበት ነጥብም ከፍ/ብሔሩ ክስ ጋር ግንኙነት የሌለው ከሆነ በወንጀል ክስ ተጠያቂ መሆን ሁልጊዜ በፍ/ብሔር ክስ ኃላፊነትን የሚያስከትል ነው ለማለት የማይቻል ስለመሆኑ፣
የፍ/ብ/ህ/ቁ.2149
የወንጀል ህግ ቁጥር 702(2)
Download Cassation Decision