federal proclamations, regulations, directives, regional constitutions and laws.
You can search cases by number, volume, subject matter
Training and teaching materials, articles, legal forms, links to resources...
ከሥራ ክርክር ጋር በተያያዘ በፍርድ ቤት የተሰጠ ውሣኔ አስቀድሞ በሥራ ላይ የነበረን የድርጅት መዋቅርን መሰረት በማድረግ ሆኖ ጉዳዩ ለአፈፃፀም በቀረበ ጊዜ የድርጅቱ መዋቅር የተለወጠ መሆኑ ከተረጋገጠ ፍርዱ ሊፈፀም የማይችል ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ.392(1),(2)
Download Cassation Decision
ለግል አገልግሎት ከቀረጥና ከታክስ ነፃ የገባን መኪና ለብድር መያዣነት መስጠት በወንጀል ኃላፊነትን (ተጠያቂነትን) የሚያስከትል ስለመሆኑ በወንጀል ጉዳይ በቅጣት መልክ የሚጣለው የገንዘብ መቀጮ በፍ/ብሔር ጉዳይ ከሚኖረው የአንድነትና የነጠላ ኃላፊነት የተለየ ስለመሆኑና ቅጣቱ በእያንዳንዱ አጥፊ ላይ ለየብቻ ሊጣል የሚገባው ስለመሆኑ፣ አዋጅ ቁ.345/95 አንቀጽ 73(1) አዋጅ ቁ. 60/89 አዋጅ ቁ.280/94 የወንጀል ህግ አንቀጽ 32(1)(ሀ), 41
ከንግድ ስም አሰጣጥ ጋር በተያያዘ የንግድ ሚኒስቴር በሚሰጠው ውሣኔ ቅሬታ ያለው ወገን አቤቱታ በይግባኝ ሊስተናገድ የሚችልበት አግባብ አዋጅ ቁ.686/2002 አንቀፅ 6, 7, 30, 2(9), 16, 61
የጋብቻ ፍቺ ውጤት በስምምነት በሚያልቅበት ወይም በሽማግሌዎች ወይም በባለሞያዎች በሚወሰንበት ጊዜ ውሣኔው ተፈፃሚነት የሚኖረው ለፍ/ቤት ቀርቦ ተቀባይነትን ሲያገኝ ብቻ ስለመሆኑ ፍቺን እና የፍቺን ውጤት በተመለከተ ውሣኔ የመስጠትና የማፅደቅ ስልጣን የፍ/ቤት ብቻ ስለመሆኑ፣ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁ.213/92 አንቀፅ 83(3), 117 የኦሮሚያ ብ/ክ/መ/የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁ.69/95 እና አዋጅ ቁ.83/96 አንቀፅ 110(5)
ህንፃን (ቤትን) በኪራይ ይዞ የሚገለገል ወገን ለአከራዩ ከሚከፍለው የኪራይ ዋጋ ላይ በህግ የተመለከተውንና ለመንግስት ገቢ ሊሆን የሚገባውን ግብር ተቀናሽ ለማድረግ ስለመቻሉና ይህንን ለማድረግም የግዴታ የፍ/ቤት ውሣኔ የማያስፈልገው ስለመሆኑ በፍርድ የኪራይ ዋጋን ለአከራይ እንዲከፍል የተወሰነበት ተከራይ ለመንግስት የሚከፈልና ከተከፋይ ሂሳቦች ላይ ግብርን ቀንሶ እንዲያስቀር የተጣለበትን ግዴታ መወጣት ያለበት በመሆኑ ሙሉውን የኪራይ ዋጋ ለአከራዩ እንዲያስረክብ በአፈፃፀም ሊገደድ ስላለመቻሉ አዋጅ ቁ.286/94 አንቀፅ 91, 101, 53(1) ደንብ ቁጥር 78/94 አንቀፅ 24, 2(ሸ)
በተዋዋይ ወገኖች መካከል ውል ባለመፈፀሙ ምክንያት የጉዳት ኪሣራ እንዲከፈል በሚል ጥያቄ በቀረበ ጊዜ በውሉ ለዚሁ ዓላማ ተዋዋዮቹ ካመለከቱት የገንዘብ መጠን በላይ እንዲከፍል ለማስገደድ የማይቻል ስለመሆኑ፣ የመልካም ሥራ አፈፃፀም ቦንድ መሰረታዊ ዓላማ በውል የተመለከተው ጉዳይ እንደውሉ ስለመፈፀሙ (የሚፈፀም ስለመሆኑ) ለማረጋገጥ ስለመሆኑ፣ አንድን ዕቃ ማቅረብ ጋር በተያያዘ የተደረገ ውልን አስመልክቶ በአቅራቢው በኩል ከእቃው ዋጋ ጋር በተገናኘ በመንግስት የታወቀ የዋጋ ግሽበት መከሰቱ አቅራቢው ውሉን ሙሉ ለሙሉ ለማቋረጥ የሚያስችለው በቂ ምክንያት ነው ለማለት የማይቻል ስለመሆኑ፣ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 3183(2),3188(1),1731,1734,1732,1889
የገጠር መሬት ባለይዞታነትን በማረጋገጥ የተሰጠ የምስክር ወረቀት የመጨረሻና የማይስተባበል ማስረጃ ነው ለማለት የማይቻል ስለመሆኑ የአማራ ብ/ክ/መ/አዋጅ ቁ.133/99 አንቀፅ 24(4) ደንብ ቁ.51/99 አንቀፅ 20(4)
የግንባታና የኮንስትራክሽን ማዕድን ማውጣት ሥራ ጋር በተያያዘ በሚመለከተው የመንግስት አካል የተሰጠ የፀና ፈቃድ ሣይኖር ከጉዳዩ ጋር በተያያዘ የመግዛትና የመሸጥ ውል መፈፀም በወንጀል ተጠያቂነትን ሊያስከትል ስለመቻሉ ህገ ወጥ ወይም ወንጀል ስለመሆኑ የተደነገገ ጉዳይ ጋር በተያያዘ የተደረጉ ውለታዎችን (ውሎችን) በህግ ኃይል እንዲፈፀሙ በሚል ለፍ/ቤት ጥያቄውን በቀረበ ጊዜ ዳኞች ጥያቄውን ውድቅ ማድረግ የሚገባቸው ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ.1718, 1716 የወ/ህ/ቁ.353(1)(ለ) አዋጅ ቁ.52/85 አንቀፅ 53(5) ደንብ ቁ.182/86 አንቀፅ 39
የንግድ ፈቃድ መብትን መጣስ በአዋጅ ቁ. 501/98 መሰረት የወንጀል ተጠያቂነትን ስለሚያስከትልበት አግባብ
እንደ ውል አልተፈፀመልኝም በሚል የጉዳት ኪሣራ ጥያቄ በቀረበ ጊዜ ፍ/ቤቶች የጥያቄ አቅራቢውን ተነፃፃሪ የውል ግዴታ ግምት ውስጥ በማስገባት የጉዳት ኪሣራ ሊወሰኑ የሚገባ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ 1771, 1802
ግብር ከፋይ የሆነ ወገን ምንም አይነት የሂሣብ መዝገብና ሰነድ ያልያዘ እንደ ሆነ ወይም በማናቸውም ምክንያት የሂሣብ መዝገቡንና ሰነዱን የግብር አስገቢው ባለስልጣን ያልተቀበለው እንደሆነ ሊከፈል የሚገባው የግብር መጠን በግምት ሊወሰን ስለመቻሉ አዋጅ ቁ.286/94 አንቀፅ 69(1), 71
የደረሰን ጉዳት ከመካስ ጋር በተገናኝ በንግድ ህጉ እውቅና ስለተሰጣቸው የመድን ሽፋን (የኢንሹራንስ ውል) አይነቶችና ባህሪያት ለንብረት የሚሰጥ የኢንሹራንስ ሽፋን አደጋው በደረሰበት ጊዜ ንብረቱ የነበረውን ዋጋ ለመካስ የሚያስችል መሆን ያለበት ስለመሆኑ፣ የንግድ ህግ ቁ. 654(2)(3),657, 674, 675, 688, 665, 678, 681, 680
Page 92 of 116