ተከራካሪ ወገኖች በአንድ የሰነድ ማስረጃ ላይ የተመለከተን ፊርማ የማን ስለመሆኑ በሚመለከተው የመንግስት አካል ተጣርቶ ውጤቱ ከቀረበና ከታወቀ በኋላ ሰነዱ በውጭ አገር ተመርምሮ ውጤቱ እንዲታወቅ በማለት የሚያቀርቡት ጥያቄ በህግ አግባብ አጥጋቢና አሣማኝ ምክንያትን በመጥቀስና በማስረጃ አስደግፈው ያላቀረቡ እንደሆነ ጥያቄው ተቀባይነት ሊኖረው የማይቻል ስለመሆኑ፣ የፍ/ቤት የተሰጠ ትእዛዘ /ውሣኔ/ መሠረታዊ የህግ ስህተት የተፈፀመበት ነው ለማለት የሚቻለው በተከራካሪ ወገኖች ፍትህ የማግኘት መብት ላይ መሠረታዊ ለውጥ የሚያስከትል እንደሆነ ስለመሆኑ፣ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 2008, 2007, 2001, 2005