የጉምሩክ ባለስልጣን ኮንትሮባንድ እንደተፈፀመበት በበቂ ሁኔታ የጠረጠረውን ተሽከርካሪ በቁጥጥሩ ሥር አድርጐ ለሚያደርገው ማጣራት ለባለንብረቱ የተቋረጠ ጥቅም እንዲከፈል የማይጠየቅ ስለመሆኑ ባለስልጣኑ በቁጥጥሩ ሥር የሚያውላቸው ተሽከርካሪዎች የተያዙበትን ጉዳይ ለማጣራት ከሚያስፈልገው ተገቢና ምክንያታዊ ጊዜ በላይ የሆነ እንደሆነ የሚያስጠይቀው ስለመሆኑ በባለስልጣኑ ቁጥጥር ሥር የቆዩ ተሽከርካሪዎችን በተመለከተ የተቋረጠ ገቢ ይከፈለን በሚል አቤቱታ በቀረበ ጊዜ ፍርድ ቤት የተጠየቀውን ገቢ ህጋዊነት እና ትክክለኛነት በማረጋገጥ መወሰን ያለበት ስለመሆኑ