federal proclamations, regulations, directives, regional constitutions and laws.
You can search cases by number, volume, subject matter
Training and teaching materials, articles, legal forms, links to resources...
ከሥራ ክርክር ጋር በተያያዘ አሰሪና የሥራ መሪ የሆነ ሰው መካከል የሚፈጠርን አለመግባባት ለመፍታት ተፈፃሚነት ያለው ደንብ (መመሪያ) በስምምነት የተዘጋጀ እንደሆነ ይሄው ደንብ ተፈፃሚ ሊደረግ የሚገባ ስለመሆኑ
Download Cassation Decision
አንድ ሰው በወንጀል ህጉ አንቀጽ 407 መሰረት በስልጣን ያለአግባብ መገልገል ወንጀል ጥፋተኛ ተደርጐ ቅጣት ሊጣልበት የሚችልበት አግባብ፣ የመ/ህ/ቁ 407(1)(ሀ)
የመንግስት ሰራተኛ ሳይሆኑ ነገር ግን ከመንግስት ሰራተኞች ጋር የጥቅም ትስስር በመፍጠር በህዝብና በመንግስት ጥቅም ላይ ጉዳት ማድረስ በሙስና ወንጀል ሊያስጠይቅ የሚችል ስለመሆኑ አዋጅ ቁ.434/97 አንቀፅ 7 የወ/ህ/ቁ.407(1)(ሀ),33
ከመንግስት አስተዳደር መ/ቤት ጋር የሥራ ውል ያደረገ ወገን እንደውሉ ለመፈፀም ባልቻለ ጊዜ የአስተዳደር መ/ቤቱ ተዋዋዩ ለውል ማስከበሪያ (contract security) በሚል ካስያዘው ገንዘብ ላይ ውሉ ባለመፈፀሙ የደረሰበትን የጉዳት ኪሣራ መቀነስ የሚችል ስለመሆኑ አዋጅ ቁ. 430/97 አንቀጽ 43 የመንግስት የግዢ መመሪያ ቁ. 117/5/ /ሀ-ሐ/
አንድን ሥራ ለሥራ ተቋራጭ የሰጠ የመንግስት መ/ቤት በራሱ ጥፋት ጉዳት አድርሶ ከሆነ ወይም የሥራ ተቋራጩን ሥራ መደበኛ አፈፃፀም ከባድ ያደረገበት እንደሆነ ለሥራ ተቋራጩ ኪሣራ የመክፈል ኅላፊነት የሚኖርበት ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህ/ቁ. 3259
ፍ/ቤቶች በባንክ ለተሰጠ ብድር መያዣነት የተሰጠ ንብረትን በአዋጅ ቁ. 97/90 ባንኩ ሲረከበው በብድሩ ገንዘብ እና በንብረቱ ወቅታዊ የዋጋ ግምት መካከል ያለውን ልዩነት ማስላት አስፈላጊ መሆኑን ባመኑ ጊዜ ይህንን ለማድረግ ልዩ የሂሳብ አዋቂ (expert witness) በመመደብ ለጉዳዩ እልባት ሊሰጡ የሚገባ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 136/1//2/
ፍ/ቤት በወንጀል ጉዳይ የተከሰሰን ሰው በተመለከተ አስቀድሞ የፈቀደውን የዋስትና መብት በራሱ አነሳሽነት ወይም በማናቸውም ባለጉዳይ አመልካችነት አዲስ ነገር ተከስቷል ብሎ ካመነ ዋስትናው እንዲነሳ ትዕዛዝ ሊሰጥ የሚችል ስለመሆኑ የወ/መ/ህ/ሥ/ሥ/ቁ. 74
የፍ/ብ/ህ/ቁ 2024(ረ) ድንጋጌ ከስልክ አገልግሎት ክፍያ ጋር በተያያዘ ተፈፃሚነት የሌለው ስለመሆኑ፣ የፍ/ብ/ህ/ቁ 2024(ረ), 2023, 2022
የጋብቻ ፍቺን በተመለከተ በፍ/ቤት የተሰጠ ውሣኔ ከሌለ በስተቀር የባልና ሚስት የጋራ ንብረትን አስመልክቶ የፍቺ ውጤት የሆነውን የክፍፍል ጥያቄ በፍ/ቤት ማቅረብ አይቻልም ለማለት የሚያስችል የህግ አግባብ የሌለ ስለመሆኑ የተሻሻለው የቤተሰብ ህግ አዋጅ ቁ.213/92 አንቀፅ 76
ስጦታ አድራጊው ሞት በኋላ ተፈፃሚ የሚሆን የስጦታ ውልን በተመለከተ ስለ ኑዛዜ የተደነገጉት ድንጋጌዎች ተፈፃሚነት ያላቸው ስለመሆኑ፣ የማይንቀሳቀስ ንብረትን አስመልክቶ የሚደረግ ስጦታ በህጉ በግልጽ የሚደረግ ኑዛዜ አስራርን በተከተለ መልኩ መደረግ ያለበት ስለመሆኑ፣ የፍ/ብ/ህ/ቁ.881, 2428, 2443, 2436
በሥር ፍ/ቤት ቀርቦ የተሰጠ ውሣኔ ለይግባኝ ሰሚ ፍ/ቤት ቀርቦ በተወሰነ መልኩ ተሻሽሎ መወሰኑ በጉዳዩ ቅር የተሰኘ ወገን ውሣኔውን አስመልክቶ ለሰበር ችሎት የሚያቀርበው አቤቱታ የመጨረሻ ፍርድ ያልተሰጠበት ነው ለማለት የማይቻል ስለመሆኑ የትግራይ ብ/ክ/መ/ አዋጅ ቁ.93/97 አንቀፅ 30(2)(ሀ), አዋጅ ቁ.49/94 አንቀፅ 16(ለ) እና 17
ከሥራ ክርክር ጋር በተያያዘ ለሠራተኛ የሚከፈል የሥራ ስንብትና ካሣ ክፍያ ላይ የገቢ ግብር ሊቀነስ የሚገባ ስለመሆኑ አዋጅ ቁ.286/94 አንቀፅ 13, 10(2), 2(10) ደንብ ቁ.78/94
Page 83 of 116