አንድ መዝገብ ላይ የተከሰሱ ሰዎች የኃላፊነት ምንጩ ከተለያየ የህግ ማዕቀፍ (ክፍል) በሆነ ጊዜ አንደኛው ወገን የተነሣው የይርጋ ክርክር በሌላኛው ወገን እንደተነሣ የማይቆጠር ስለመሆኑ፣ በአንድ ክስ (መዝገብ) ተጣምረው በአንድነት እና በነጠላ ኃላፊነት አለባችሁ ተብለው ከተከሰሱ ወገኖች መካከል አንደኛው ወገን የሚያነሣው የይርጋ መቃወሚያ ያለቅድመ ሁኔታ በሌላኛው ተጣምሮ የተከሰሰው ወገን ላይ ተፈፃሚነት አለው ለማለት የማይቻል ስለመሆኑ፣ በፍ/ብሔር ጉዳይ የአንድነትና የነጣላ ኃላፊነት ከተለያዩ የህግ ክፍሎች እና ከተለያዩ ምክንያቶች ሊመነጭ የሚችል ስለመሆኑ፣ የፍ/ብ/ህ/ቁ.1852 የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ.244(3),36