በአንድ ጉዳይ በከሳሽነትና በተከሳሽነት በተሰየሙ ወገኖች መካከል በተካሄደ ክርክር የተሰጠ ፍርድ ጋር በተያያዘ መብት ወይም ጥቅም አለኝ የሚል ወገን ወይም እርሱ ባልተካፈለበት ሁኔታ በመካሄድ ላይ ባለ ክርክር መብቱ/ጥቅሙ የሚጐዳበት ሰው በክርክሩ በመግባት መብቱን በህግ አግባብ ሊያስከብር ስለሚችልበት ሁኔታ፣ ከላይ በተመለከተውና ባልተካፈልኩበት ክርክር የተሰጠ ፍርድ ሥርዓትን ባለመከተል የተሰጠ ነው በሚል ምክንያት ብቻ ፍርዱ ዋጋ እንዲያጣ ወይም አንዴ የተሰጠ ፍርድን ወደ ጐን በመተው በሌላ ጊዜ በሚሰጥ አዲስ ፍርድ እንዲቀየር ለማድረግ የሚያስችል የህግ አግባብ የሌለ ስለመሆኑ፣ የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህቁ. 41, 358, 212