ከውል አመስራረትና መቋቋም ጋር በተገናኘ ዝምታ በመርህ ደረጃ ውልን እንደመቀበል ሊቆጠር የማይችል ስለመሆኑና አንድ ውል፣ ተሻሽሏል ለማለት የሚቻለው ማሻሻያው አስቀድሞ በተደረገው የአፃፃፍ ስርዓት አይነት የተከናወነ እንደሆነ ስለመሆኑ፣ የግልግል ጉባኤ አንድን ጉዳይ በማየት የዳኝነት መፍትሔ ሊሰጥ የሚችለው ተከራካሪ ወገኖች ከተስማሙበትና የሚፀና ወይም ዋጋ ያለው ግዴታ መኖሩን መሠረት በማድረግ ስለመሆኑ፣ የፍ/ብ/ህ/ቁ.1682,1683,1684,1722,2001 የፍ/ብ/ሥ/ሥ/ህ/ቁ. 356(ሀ)